አዝ፦ ልቤ ፡ ፀና
ልቤ ፡ በአንተ ፡ ፀና (፪x)
ቃልህን ፡ ይዣለሁ ፡ ባይታይ ፡ ደመና
ዘምር ፡ ዘምር ፡ አለኝ ፡ ልቤ ፡ በአንተ ፡ ፀና
አዝ፦ ልቤ ፡ ፀና
ልቤ ፡ በአንተ ፡ ፀና (፪x)
ሳይቀየር ፡ ሁሉ ፡ እንዳለ ፡ ሆኖ
ሲያመሰግን ፡ በአምላኩ ፡ ተማምኖ
ምድረበዳን ፡ የሚያለመልመው
በረሃውን ፡ ገነት ፡ አደረገው
ሳይቀየር ፡ ሁሉ ፡ እንዳለ ፡ ሆኖ
ሲያመሰግን ፡ በአምላኩ ፡ ተማምኖ
ምድረበዳን ፡ የሚያለመልመው
ድንገት ፡ ደርሶ ፡ ታሪኩን ፡ ቀየረው
አዝ፦ ልቤ ፡ ፀና
ልቤ ፡ በአንተ ፡ ፀና (፪x)
ቃልህን ፡ ይዣለሁ ፡ ፡ ባይታይ ፡ ደመና
ዘምር ፡ ዘምር ፡ አለኝ ፡ ልቤ ፡ በአንተ ፡ ፀና
አዝ፦ ልቤ ፡ ፀና
ልቤ ፡ በአንተ ፡ ፀና (፪x)
በገናዬ ፡ ከተሰቀለበት
ይውረድና ፡ ቅኔን ፡ ልቀኝበት
ሁኔታው ፡ ሳይቀያየር
አውቅበት ፡ የለ ፡ ለአንተ ፡ መዘምር
በገናዬ ፡ ከተሰቀለበት
ይውረድ ፡ እንጂ ፡ ቅኔን ፡ ልቀኝበት
ሁኔታው ፡ ሳይቀያየር
አውቅበት ፡ የለ ፡ ለአንተ ፡ መዘምር
ምሥጋና ፡ ለሥምህ
ምሥጋና ፡ ለክብርህ
ይገባሃል ፡ ጌታ
አይጓደለብህ
ዝማሬ ፡ ለሥምህ
ዝማሬ ፡ ለክብርህ
ይገባሃል ፡ አንተስ
አይጓደለብህ
ባያድነን ፡ እኛስ ፡ ለአንተ ፡ አንሰግድም
ላቆመውከው ፡ ምስል ፡ ፈፅሞ ፡ እጅ ፡ አንሰጥም
ሰባት ፡ እጥፍ ፡ ቢነድም ፡ እሳቱ
ይመለካል ፡ የእኛስ ፡ ክንደ ፡ ብርቱ (፪x)
ምሥጋና ፡ ለሥምህ
ምሥጋና ፡ ለክብርህ
ይገባሃል ፡ ጌታ
አይጓደለብህ
ዝማሬ ፡ ለሥምህ
ዝማሬ ፡ ለክብርህ
ይገባሃል ፡ አንተስ
አይጓደለብህ
ባሪያዎችህ ፡ ወህኒ ፡ ቤት ፡ ተጥለው
ግን ፡ ሲያመልኩ ፡ ቅዱስ ፡ ቅዱስ ፡ ብለው
የወህኒውን ፡ መሠረት ፡ አናውጠህ
ተገልጠሃል ፡ እስራት ፡ በጣጥሰህ
ቅዱስ (፫x)
ጌታ ፡ ኢየሱስ
ኃያል (፫x)
የሚመስልህ ፡ ታጥቷል (፪x)
አዝ፦ ልቤ ፡ ፀና
ልቤ ፡ በአንተ ፡ ፀና (፫x)