ልጄ ፡ ሆይ ፡ ህጌን ፡ አትርሳ ፡ ልብህም ፡ ት እዛዛቴን ፡ ይጠብቅ
ብዙ ፡ ዘመናትና ፡ ረጅም ፡ ዕድሜ
ቃልህን ፡ ሰምቻለሁ ፡ ድምፅህን ፡ ሰምቻለሁ
ምክርህን ፡ ሰምቻለሁ ፡ ሰምቻለሁ
ፍሬ ፡ እንዳታጣብኝ ፡ ግን ፡ እፈራለሁ
የሚወድህ ፡ ቃልህን ፡ ይጠብቃል
ትእዛዛትህን ፡ በመንገዱ ፡ ያረጋል
ድምፅህን ፡ ሰምቼ ፡ ጌታ ፡ ካልታዘዝኩኝ
የታለ ፡ ፍቅሬ ፡ ለአንተ ፡ ያለኝ
ምክርህ ፡ ካልተቀየርኩኝ
ከክፉ ፡ ሃሳቤም ፡ ካልተመለስኩኝ
መልኬን ፡ ብቻ ፡ አይቶ ፡ መሄድ ፡ ይሆንብኛል
ታዲያ ፡ ይሄ ፡ ምን ፡ ይጠቅመኛል
ቁጣህም ፡ ሳይብስ ፡ ቅጣት ፡ ሳይመጣ ፡
ጌታ ፡ መልሰኝ ፡ ጨርሼ ፡ እንዳልወጣ
ያኔ ፡ በረከት ፡ ፍሬ ፡ ይበዛልኛል
በመታዘዜ ፡ መውደዴ ፡ ይታያል
የልቤ ፡ መሻት ፡ የውስጥ ፡ ጥማቴ
አክብሬህ ፡ መኖር ፡ እኔስ ፡ በሕይወቴ ፡
ፀጋህን ፡ እሻለሁ ፡ በዚም ፡ ደግሜ