ክበር ፡ የሆነን ፡ ጌታ ፡ ሞገስ ፡ የሆነን ፡ ጌታ
ብቃት ፡ የሆነን ፡ ጌታ ፡ በጉድለታችን ፡ ፈንታ
ክንዱን ፡ በዘመናችን ፡ በዓይናችን ፡ አይተነዋል
መልካም ፡ እረኛ ፡ ኢየሱስ ፡ እስከዛሬ ፡ ረድቶናል
በዘመን ፡ በአመታት ፡ መሃል ፡ የሚገዳደረው ፡ የታል
ብቻውን ፡ ድንቅ ፡ እየሰራ ፡ የሚኖር ፡ እንደተፈራ
ለእኛም ፡ ይሄው ፡ ሞገስ ፡ ሆነን ፡ ባሕሩን ፡ ከፍሎ ፡ አሻገረን
ችግራችንን ፡ እረሳነው ፡ በኢየሱስ ፡ ስንቱን ፡ አለፍን
አዝ
ክበር ፡ የሆነን ፡ ጌታ
ስንቱን ፡ ተሻገርን ፡ አለፍን ፡ በምሥጋና ፡ ሆ ፡ እያልን
ስንቱስ ፡ ከእግራችን ፡ ወደቀ ፡ በኢየሱስ ፡ እየደቀቀ
ዘመን ፡ ሲያልፍ ፡ ዘመን ፡ ሲተካ ፡ ፍሬያችን ፡ አብቦ ፡ ፈካ
የረገጥነውን ፡ ወረስን ፡ እለት ፡ እለት ፡ አማረብን
አዝ
ሞገስ ፡ የሆነን ፡ ጌታ
በምድረ ፡ በዳ ፡ በረሃ ፡ የሚያረካ ፡ ውኃ ፡ ሆነን
አልሰለቸን ፡ የእኛ ፡ ጌታ ፡ እንደቃሉ ፡ ተለመነን
በመከራ ፡ ቀን ፡ ሰቀቀን ፡ ተማምነን ፡ ስሙን ፡ ስንጠራ
ደረሰልን ፡ በሰአቱ ፡ ኢየሱስ ፡ ጌታ ፡ የሚያኮራ
አዝ
ክብር ፡ የሆነን ፡ ጌታ
ሸንጐ ፡ በእኛ ፡ ላይ ፡ ሲማከር ፡ ዲያብሎስ ፡ ሊያጠፋን ፡ ሲጥር
ማነው ፡ ደርሶ ፡ የታደገን : በመከራ : መርከብ ፡ ሆነን
ታሪክ ፡ ይናገር ፡ ብዙ ፡ ነው : ብዙ ፡ ነው ፡ እኛስ ፡ ያለፍነው
ከእግራችን ፡ ስር ፡ ወድቆ ፡ ጠላት ፡ ጭንቅላቱን ፡ ረገጥነው
አዝ
ክበር ፡ የሆነን ፡ ጌታ