የጽድቅን ፡ ጥሩር ፡ ለብሼ
ገነትም ፡ ጋሻ ፡ አንስቼ
በቃል ፡ እውነት ፡ ታጥቄ
እቆማለሁ ፡ ፀንቼ (፪x)
አዝ፦ እኔ ፡ ግን ፡ እግዚአብሔርን ፡ አመልካለሁ
በዘመኔ ፡ ሁሉ ፡ ለእርሱ ፡ እገዛለሁ (፪x)
በፍጹም ፡ ልቤ ፡ እሰግዳለሁ
ሃሳቤን ፡ አስገዛለሁ
በፈቃዴ ፡ እሸነፋለሁ
ጌታዬን ፡ አመልከዋለሁ (፪x)
አዝ፦ እኔ ፡ ግን ፡ እግዚአብሔርን ፡ አመልካለሁ
በዘመኔ ፡ ሁሉ ፡ ለእርሱ ፡ እገዛለሁ (፪x)
በጽኑ ፡ ምክሩ ፡ ታምኜ
በቅን ፡ ስርዓቱ ፡ ሄጄ
ቅዱስ ፡ ሥሙን ፡ አከብራለሁ
አምላኬን ፡ አመልከዋለሁ (፪x)
አዝ፦ እኔ ፡ ግን ፡ እግዚአብሔርን ፡ አመልካለሁ
በዘመኔ ፡ ሁሉ ፡ ለእርሱ ፡ እገዛለሁ (፪x)
እግዚአብሔርን ፡ እባርካለሁ
ምሥጋናውም ፡ ሁሉ ፡ በአፌ ፡ ነው
በእርሱ ፡ ፍቅር ፡ አኖራዋለሁ
ዘለዓለም ፡ አመልከዋለሁ
አዝ፦ እኔ ፡ ግን ፡ እግዚአብሔርን ፡ አመልካለሁ
በዘመኔ ፡ ሁሉ ፡ ለእርሱ ፡ እገዛለሁ (፬x)