Meserete Kirstos Choir-Endiet Talaq Neh (እንዴት ፡ ታላቅ ፡ ነህ)

አዝ፦ አቤት ፡ እንዴት ፡ ትላቅ ፡ ነህ
እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ
እንዴት ፡ ፍፁም ፡ ነህ
የዘለዓለም ፡ አምላክ ፡ የማትለውጥ
የፍቅር ፡ አባት ፡ ጸንተህ ፡ ትኖራለህ (፪x)

በቃ ፡ አልፈልግም ፡ ልቤን ፡ ውሰደው
አእምሮዬን ፡ ግዛው ፡ ለአንተ ፡ አድርገው
ዝም ፡ ልበልና ፡ ኃይልህን ፡ ልመልከት
ሌላው ፡ ሀሳቤ ፡ ይብቃ ፡ ይከተት

አዝ፦ አቤት ፡ እንዴት ፡ ትላቅ ፡ ነህ
እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ
እንዴት ፡ ፍፁም ፡ ነህ
የዘለዓለም ፡ አምላክ ፡ የማትለውጥ
የፍቅር ፡ አባት ፡ ጸንተህ ፡ ትኖራለህ

ሌት ፡ በመኝታ ፡ እንዳስብ ፡ አንተን
ቀን ፡ በሥራዬ ፡ እንዳጠነጥን
መና ፡ ለነፍሴ ፡ እርካታና ፡ ደስታ
ክብርህን ፡ ላስበው ፡ ሁሌ ፡ ጠዋት ፡ ማታ

አዝ፦ አቤት ፡ እንዴት ፡ ትላቅ ፡ ነህ
እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ
እንዴት ፡ ፍፁም ፡ ነህ
የዘለዓለም ፡ አምላክ ፡ የማትለውጥ
የፍቅር ፡ አባት ፡ ጸንተህ ፡ ትኖራለህ

እጄን ፡ በአፌ ፡ ላይ ፡ አድርጌ ፡ ተደነኩ
ሥራህንም ፡ ሳየው ፡ በደስታ ፡ ተሞላሁ
በእውነት ፡ ተረዳሁ ፡ የአንተን ፡ ታላቅነት
እንዲሁም ፡ አስተዋልኩ ፡ የእኔን ፡ ውዳቂነት

አዝ፦ አቤት ፡ እንዴት ፡ ትላቅ ፡ ነህ
እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ
እንዴት ፡ ፍፁም ፡ ነህ
የዘለዓለም ፡ አምላክ ፡ የማትለውጥ
የፍቅር ፡ አባት ፡ ጸንተህ ፡ ትኖራለህ

ለአንተ ፡ የሚገባህ ፡ ክብርህን ፡ ለመስጠት
በመንፈስ ፡ ሳስብህ ፡ ያኔ ፡ ተረዳሁት
አሁን ፡ ቃልኪዳኔ ፡ የመጨረሻው
ተዋርጄ ፡ እንድኖር ፡ ነው ፡ ለአንተ ፡ የምሻው

አዝ፦ አቤት ፡ እንዴት ፡ ትላቅ ፡ ነህ
እንዴት ፡ ታማኝ ፡ ነህ
እንዴት ፡ ፍፁም ፡ ነህ
የዘለዓለም ፡ አምላክ ፡ የማትለውጥ
የፍቅር ፡ አባት ፡ ጸንተህ ፡ ትኖራለህ (፪x)

Recently Listened by

0 comments
    No comments found

:: / ::
::
/ ::

Queue