አዝ፦ ታማኝነትህ ፡ ብዙ ፡ ምህረትህ ፡ ለልጅ ፡ ልጅ ፡ ነው
አንተን ፡ ተስፋ ፡ አድርጐ ፡ ያፈረ ፡ ሰው ፡ ማን ፡ ነው
ሁሉንም ፡ በስዓቱ ፡ ውብ ፡ አድርገህ ፡ ትሰራለህ
አማካሪ ፡ አትፈልግም ፡ ብቻህን ፡ ኤልሻዳይ ፡ (ኢየሱስ) ነህ
በመከራ ፡ ቀን ፡ ስምህን ፡ጠርቶ ፡ማን ፡ ከቶ ፡ አፍሮ ፡ ያውቃል
ዓይንህ ፡ ግሩም ፡ ነው ፡ በሰማይ ፡ ምስኪኑን ፡ ይመለከታል
ታማኝነትህ ፡ የበዛ ፡ ምህረትህ ፡ ወደር ፡ የሌለው
አንተን ፡ ተስፋ ፡ ላደረጉ ፡ እርግማኑ ፡ በረከት ፡ ነው
አዝ፦ ታማኝነትህ ፡ ብዙ ፡ ምህረትህ ፡ ለልጅ ፡ ልጅ ፡ ነው
አንተን ፡ ተስፋ ፡ አድርጐ ፡ ያፈረ ፡ ሰው ፡ ማን ፡ ነው
ሁሉንም ፡ በስዓቱ ፡ ውብ ፡ አድርገህ ፡ ትሰራለህ
አማካሪ ፡ አትፈልግም ፡ ብቻህን ፡ ኤልሻዳይ ፡ (ኢየሱስ) ነህ
ታላቅ ፡ ተራራ ፡ በስምህ ፡ ደልዳላ ፡ ሜዳ ፡ ይሆናል
ማዕበል ፡ ቃልህን ፡ ሰምቶ ፡ ፈጥኖ ፡ ያተዘዝልሃል
ህዝብህን ፡ በምድረበዳ ፡ መናን ፡ መመገብ ፡ ታውቃለህ
ቃልህን ፡ ለሚጠብቁ ፡ መች ፡ አንተ ፡ ታሳፍራለህ
አዝ፦ ታማኝነትህ ፡ ብዙ ፡ ምህረትህ ፡ ለልጅ ፡ ልጅ ፡ ነው
አንተን ፡ ተስፋ ፡ አድርጐ ፡ ያፈረ ፡ ሰው ፡ ማን ፡ ነው
ሁሉንም ፡ በስዓቱ ፡ ውብ ፡ አድርገህ ፡ ትሰራለህ
አማካሪ ፡ አትፈልግም ፡ ብቻህን ፡ ኤልሻዳይ ፡ (ኢየሱስ) ነህ
ደካማው ፡ጉልበቱ ፡ በአንተ ፡ ኃይሉ ፡ እንደንስር ፡ ታደሰ
ሃያሉ ፡ ሞገስህን ፡ሲያይ ፡ወኔው ፡ ሃሞቱ ፡ ፈሰሰ
ብላቴናው ግን፡ በሥምህ ፡ ወንጭፍ ፡ጠጠሩን ፡ ሰንዝሮ
አየሁ ፡ ጠላቱ፡ በቅጽበት ፡በአደባባይ ፡ ተዘርሮ
አዝ፦ ታማኝነትህ ፡ ብዙ ፡ ምህረትህ ፡ ለልጅ ፡ ልጅ ፡ ነው
አንተን ፡ ተስፋ ፡ አድርጐ ፡ ያፈረ ፡ ሰው ፡ ማን ፡ ነው
ሁሉንም ፡ በስዓቱ ፡ ውብ ፡ አድርገህ ፡ ትሰራለህ
አማካሪ ፡ አትፈልግም ፡ ብቻህን ፡ ኤልሻዳይ ፡ (ኢየሱስ) ነህ
ሰማይን ፡ ምድርን ፡ ስትራ ፡ ማን ፡ ቀርቦ ፡ አንተን ፡ አማክሯል
ኤልሻዳይ ፡ ጌታ ፡ መሆንህን ፡ ፍጥረት ፡ ሁሉ ፡ ይመሰክራል
ብቻህን ፡ ለዘለዓለም ፡ ጸንተህ ፡ በዙፋንህ ፡ ላይ ፡ ነህ
አንተን ፡ ታምኘ ፡ እስከዛሬ ፡ ማድጋዬ ፡ መች ጐደለ
አዝ፦ ታማኝነትህ ፡ ብዙ ፡ ምህረትህ ፡ ለልጅ ፡ ልጅ ፡ ነው
አንተን ፡ ተስፋ ፡ አድርጐ ፡ ያፈረ ፡ ሰው ፡ ማን ፡ ነው
ሁሉንም ፡ በስዓቱ ፡ ውብ ፡ አድርገህ ፡ ትሰራለህ
አማካሪ ፡ አትፈልግም ፡ ብቻህን ፡ ኤልሻዳይ ፡ (ኢየሱስ) ነህ