Meserete Kirstos Choir-Amlakie Yaderegewn Neger (አምላኬ ፡ ያደረገውን ፡ ነገር)

አዝ፦ አምላኬ ፡ ያደረገውን ፡ ሁሉ ፡ ባወራው
ባወራው ፡ ባወራው ፡ ባወራው
ከቁጥር ፡ ሁሉ ፡ በዛ ፡ ተዓምራቱ
ብዙ ፡ ነው ፡ ባወራው (፪x)

ኃጢአተኛ ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ ብሎ ፡ አይቼ
እንደ ፡ ሊባኖስ ፡ ዛፍ ፡ ለምልሞ ፡ ፈርቼ
ተመልሼ ፡ ከቦታው ፡ ፈለግሁት
እንኳን ፡ እርሱን ፡ ስፍራውን ፡ አጣሁት

አዝ፦ አምላኬ ፡ ያደረገውን ፡ ሁሉ ፡ ባወራው
ባወራው ፡ ባወራው ፡ ባወራው
ከቁጥር ፡ ሁሉ ፡ በዛ ፡ ተዓምራቱ
ብዙ ፡ ነው ፡ ባወራው (፪x)

የክፉ ፡ ኃይል ፡ በቁጣ ፡ ዓይኖቼ ፡ እያየኝ
ጥርሱን ፡ በላዬ ፡ ላይ ፡ ስያንገጫግጭብኝ
እግዚአብሔር ፡ ግን ፡ አይቶ ፡ ስቆበታል
የመትፍያው ፡ ቀን ፡ እንደደረሰ ፡ አውቋል

አዝ፦ አምላኬ ፡ ያደረገውን ፡ ሁሉ ፡ ባወራው
ባወራው ፡ ባወራው ፡ ባወራው
ከቁጥር ፡ ሁሉ ፡ በዛ ፡ ተዓምራቱ
ብዙ ፡ ነው ፡ ባወራው (፪x)

ከመቅደሱ ፡ ከሰማይ ፡ ከፍታ ፡ ላይ ፡ ሆኗል
ወደ ፡ ምድር ፡ በታች ፡ አሽቆልቁሎ ፡ አይቷል
የእስረኞቹን ፡ የጩኸት ፡ ቃል ፡ ሰምቷል
ከሞት ፡ አፋፍ ፡ ከፍርድ ፡ ወጥመድ ፡ ፈቷል

አዝ፦ አምላኬ ፡ ያደረገውን ፡ ሁሉ ፡ ባወራው
ባወራው ፡ ባወራው ፡ ባወራው
ከቁጥር ፡ ሁሉ ፡ በዛ ፡ ተዓምራቱ
ብዙ ፡ ነው ፡ ባወራው (፪x)

ከሰይጣን ፡ ኃይል ፡ የዳንህ ፡ ወገን ፡ ሁሉ ፡ ከሰይፍ
ለሚመጣው ፡ ትውልድ ፡ ጻፍና ፡ አስተላልፍ
አምላካችን ፡ ይህን ፡ ተአምር ፡ ሰርቷል
እኔም ፡ ባወራ ፡ ባወራው ፡ በዝቷል

አዝ፦ አምላኬ ፡ ያደረገውን ፡ ሁሉ ፡ ባወራው
ባወራው ፡ ባወራው ፡ ባወራው
ከቁጥር ፡ ሁሉ ፡ በዛ ፡ ተዓምራቱ
ብዙ ፡ ነው ፡ ባወራው (፪x)

Recently Listened by

0 comments
    No comments found

:: / ::
::
/ ::

Queue