Abeqa (አበቃ)

አበቃ ፡ አከተመ ፡ በተባለ ፡ ጊዜ
ማነው ፡ ለእኔስ ፡ ፈጥኖ ፡ የደረሰው (፪x)

ጌታ ፡ እኮ ፡ ነው
ጌታ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ አሃ (፫x)
ጌታ ፡ እኮ ፡ ነው
ይህን ፡ ያደረገው

እስራቴን ፡ ፈተህ ፡ ቀንበሬን ፡ ሰብረህ
ያስጨነቀኝ ፡ ጠላት ፡ ከእግሬ ፡ ሥር ፡ ጥለህ
ዛሬማ ፡ ቀና ፡ አልኩኝ ፡ ይኸው ፡ በኢየሱስ
ዘለዓለም ፡ ልገዛ ፡ ልስገድልህ (፪x)

አምላክ ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ
ረዳት ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ
አባት ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ
ረዳት ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ

ሲረዳኝ ፡ በዓይኔ ፡ እያየሁ
ሲያግዘኝ ፡ በዓይኔ ፡ እያየሁ (፪x)

ሥምህን ፡ ጠርቼ ፡ ሁሉን ፡ አለፍኩ
መቼ ፡ አንተን ፡ ይዤ ፡ እኔስ ፡ አፈርኩ
ዛሬም ፡ የሚያቅተኝ ፡ ሁሉ
እወጣዋለሁ ፡ የአንተ ፡ ነው ፡ ኃይሉ (፪x)

አበቃ ፡ አከተመ ፡ በተባለ ፡ ጊዜ
ማነው ፡ ለእኔስ ፡ ፈጥኖ ፡ የደረሰው (፪x)

ጌታ ፡ እኮ ፡ ነው
ጌታ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ አሃ (፫x)
ጌታ ፡ እኮ ፡ ነው
ይህን ፡ ያደረገው

አምላክ ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ
ረዳት ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ
አባት ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ
ረዳት ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ

ሲረዳኝ ፡ በዓይኔ ፡ እያየሁ
ሲያግዘኝ ፡ በዓይኔ ፡ እያየሁ (፪x)

Recently Listened by

0 comments
    No comments found

እዚህ ያስተዋውቁ!

Live Podcast

Sponsored Ads



:: / ::
::
/ ::

Queue