አዝ፦ አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
አገራችንን ፡ አስፋ
እጅህም ፡ በእኛ ፡ ላይ ፡ ትሁን
አንተ ፡ ነህ ፡ የእኛ ፡ ተስፋ
ያቤጽንም ፡ ሰምተሃል ፡ እንደዚህ ፡ ሲለምንህ
ነፍሱን ፡ ባርከህለታል ፡ አገሩንም ፡ አስፍተህ
አዝ፦ አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
አገራችንን ፡ አስፋ
እጅህም ፡ በእኛ ፡ ላይ ፡ ትሁን
አንተ ፡ ነህ ፡ የእኛ ፡ ተስፋ
በልጅህ ፡ ስቃይና ፡ በጣር ፡ የተወለድን
እኛም ፡ ፍሬዎችህ ፡ ነን ፡ አስባስበህ ፡ ጠብቀን
አዝ፦ አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
አገራችንን ፡ አስፋ
እጅህም ፡ በእኛ ፡ ላይ ፡ ትሁን
አንተ ፡ ነህ ፡ የእኛ ፡ ተስፋ
ከፊትህ ፡ አትጣለን ፡ እንማጸንሃለን
በሞገስህ ፡ አስበን ፡ በምህረትህ ፡ ጐብኘን
አዝ፦ አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
አገራችንን ፡ አስፋ
እጅህም ፡ በእኛ ፡ ላይ ፡ ትሁን
አንተ ፡ ነህ ፡ የእኛ ፡ ተስፋ
ሰማያቱም ፡ ይከፈቱ ፡ መንፈስህ ፡ ይፍሰስልን
ሕይወታችን ፡ ትረስርስ ፡ ነፍሳችን ፡ ትጥገብልን
አዝ፦ አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
አገራችንን ፡ አስፋ
እጅህም ፡ በእኛ ፡ ላይ ፡ ትሁን
አንተ ፡ ነህ ፡ የእኛ ፡ ተስፋ
ብቻችንን ፡ አንቅር ፡ አብዛን ፡ እየባረክህ
አበልጽገን ፡ በፀጋህ ፡ ታደገን ፡ በቃልህ
አዝ፦ አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
አገራችንን ፡ አስፋ
እጅህም ፡ በእኛ ፡ ላይ ፡ ትሁን
አንተ ፡ ነህ ፡ የእኛ ፡ ተስፋ
እግዚአብሔርን ፡ በማወቅ ፡ ምድር ፡ እስክትሞላ
ምልጃችን ፡ ይቀጥላል ፡ ጉልበታችን ፡ ሳይላላ
አዝ፦ አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
አገራችንን ፡ አስፋ
እጅህም ፡ በእኛ ፡ ላይ ፡ ትሁን
አንተ ፡ ነህ ፡ የእኛ ፡ ተስፋ