Misgana Yemigebawin (ምሥጋና ፡ የሚገባውን)

<poem>
:<u>አዝ</u>፦ ምሥጋና ፡ የሚገባውን
::እግዚአብሔርን ፡ እጠራለሁ
::ከጠላቶቼም ፡ እድናለሁ (፪x)

የአመጽ ፡ ፈሳሽ ፡ ሲያስፈራራኝ ፡ የሲዖል ፡ ጣርም ፡ ሲከበኝ
አምላክህ ፡ የታለ ፡ ሲለኝ ፡ ባላንጣዬ ፡ ሲያፌዝብኝ
ከመሠረቴ ፡ ሊነቅለኝ ፡ ቆይ ፡ ብቻ ፡ ሲል ፡ ሲዝትብኝ
የጌታን ፡ ሥም ፡ እጠራለሁ ፡ ከጠላቴም ፡ እድናለሁ

:<u>አዝ</u>፦ ምሥጋና ፡ የሚገባውን
::እግዚአብሔርን ፡ እጠራለሁ
::ከጠላቶቼም ፡ እድናለሁ (፪x)

የጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ለእኔ ፡ የፀና ፡ ግንብ ፡ ነውና
እስከዛሬም ፡ እርሱን ፡ ጠርቶ ፡ ማንም ፡ አላፈረምና
በኪሩቤል ፡ የሚኖረው ፡ ሙሉ ፡ ተስፋ ፡ ስለሰጠኝ
ታምኜ ፡ ሥሙን ፡ እጠራለሁ ፡ ከጠላቴም ፡ እድናለሁ

:<u>አዝ</u>፦ ምሥጋና ፡ የሚገባውን
::እግዚአብሔርን ፡ እጠራለሁ
::ከጠላቶቼም ፡ እድናለሁ (፪x)

በጨነቀኝ ፡ ጊዜ ፡ ሁሉ ፡ እግዚአብሔርን ፡ ጠራሁት
ስቅስቅ ፡ እያልኩኝ ፡ በእንባ ፡ የሆዴን ፡ ብሶት ፡ ነገርኩት
ከዚያም ፡ በበቀል ፡ ወረደ ፡ ከሰማይ ፡ አንጐደጐደ
በመብረቁ ፡ አወካቸው ፡ በፍላጻው ፡ በተናቸው

:<u>አዝ</u>፦ ምሥጋና ፡ የሚገባውን
::እግዚአብሔርን ፡ እጠራለሁ
::ከጠላቶቼም ፡ እድናለሁ (፪x)

ለጥርሶቻቸው ፡ ንክሻ ፡ አላደረገኝምና
ከተዘረጋብኝ ፡ ወጥመድ ፡ ሁሌ ፡ አድኖኛልና
አርነቴን ፡ ከሚቀማ ፡ ከሰይጣን ፡ ጋርዶኛልና
ሥሙ ፡ ይክበር ፡ ሃሌሉያ ፡ እያልኩኝ ፡ ልኑር ፡ በእርሱ ፡ ጉያ

:<u>አዝ</u>፦ ምሥጋና ፡ የሚገባውን
::እግዚአብሔርን ፡ እጠራለሁ
::ከጠላቶቼም ፡ እድናለሁ (፪x)
</poem>

Recently Listened by

0 comments
    No comments found

እዚህ ያስተዋውቁ!

Live Podcast

Sponsored Ads



:: / ::
::
/ ::

Queue