መዳኔ ፡ ሲገርመኝ (Medanie Sigermegne) - ለዓለም ፡ ጥላሁን

መዳኔ ፡ ሲገርመኝ ፡ አይኔ ፡ መከፈቱ
ደግሞ ፡ ታምራትህ ፡ በዛ ፡ በየእለቱ (፪x)
አንተን ፡ አመስግኜ ፡ ማቋረጥ ፡ አልችልም
ውስጤ ፡ የገባው ፡ ፍቅርህ ፡ ዝም ፡ አያሰኘኝም
ዝም ፡ አያሰኘኝም (፪x)

አዝ:- ዓይኖቼንም ፡ እያበራህ ፡ ጉልበቴንም ፡ እያጸናህ
ወደ ፡ ፊት ፡ እያራመድከኝ ፡ በድል ፡ ላይ ፡ ድልን ፡ ሰጠኅኝ
በእውነት ፡ አንተ ፡ ጌታ ፡ ነህ ፡ ምስጋናዬም ፡ ይድረስህ
በእውነት ፡ አንተ ፡ ንጉስ ፡ ነህ ፡ አምልኮዬም ፡ ይድረስህ
በእውነት ፡ አንተ ፡ ጌታ ፡ ነህ ፡ ምስጋናዬም ፡ ይድረስህ
በእውነት ፡ አንተ ፡ ንጉስ ፡ ነህ ፡ አምልኮዬም ፡ ይድረስህ (፪x)

መዘመር ፡ ለአንተ ፡ ነው ፡ ማምለክም ፡ አንተን
ድንቅን ፡ እየሰራህ ፡ ለምታኖረን (፪x)
እንዲያው ፡ ክበር ፡ እንጂ ፡ ሌላ ፡ ምን ፡ ይባላል
ጌታ ፡ ያንተ ፡ ፍቅር ፡ ክመታወቅ ፡ ያልፋል
ክመታወቅ ፡ ያልፋል (፪x)

አዝ:- ዓይኖቼንም ፡ እያበራህ ፡ ጉልበቴንም ፡ እያጸናህ
ወደ ፡ ፊት ፡ እያራመድከኝ ፡ በድል ፡ ላይ ፡ ድልን ፡ ሰጠኅኝ
በእውነት ፡ አንተ ፡ ጌታ ፡ ነህ ፡ ምስጋናዬም ፡ ይድረስህ
በእውነት ፡ አንተ ፡ ንጉስ ፡ ነህ ፡ አምልኮዬም ፡ ይድረስህ
በእውነት ፡ አንተ ፡ ጌታ ፡ ነህ ፡ ምስጋናዬም ፡ ይድረስህ
በእውነት ፡ አንተ ፡ ንጉስ ፡ ነህ ፡ አምልኮዬም ፡ ይድረስህ (፪x)

አንተው ፡ በሰጠህኝ ፡ በዚች ፡ አንደበቴ
እባርክሃለሁ ፡ ክበር ፡ መድኃኒቴ (፪x)
ከልብ ፡ የፈለቀ ፡ የምስጋና ፡ ዜማ
ይሄው ፡ አምጥቻለሁ ፡ በፊትህ ፡ ላሰማ
በፊትህ ፡ ላሰማ (፪x)

አዝ:- ዓይኖቼንም ፡ እያበራህ ፡ ጉልበቴንም ፡ እያጸናህ
ወደ ፡ ፊት ፡ እያራመድከኝ ፡ በድል ፡ ላይ ፡ ድልን ፡ ሰጠኅኝ
በእውነት ፡ አንተ ፡ ጌታ ፡ ነህ ፡ ምስጋናዬም ፡ ይድረስህ
በእውነት ፡ አንተ ፡ ንጉስ ፡ ነህ ፡ አምልኮዬም ፡ ይድረስህ
በእውነት ፡ አንተ ፡ ጌታ ፡ ነህ ፡ ምስጋናዬም ፡ ይድረስህ
በእውነት ፡ አንተ ፡ ንጉስ ፡ ነህ ፡ አምልኮዬም ፡ ይድረስህ (፪x)

መዳኔ ፡ ሲገርመኝ ፡ አይኔ ፡ መከፈቱ
ደግሞ ፡ ታምራትህ ፡ በዛ ፡ በየእለቱ (፪x)
አንተን ፡ አመስግኜ ፡ ማቋረጥ ፡ አልችልም
ውስጤ ፡ የገባው ፡ ፍቅርህ ፡ ዝም ፡ አያሰኘኝም (፪x)

መዘመር ፡ ለአንተ ፡ ነው ፡ ማምለክም ፡ አንተን
ድንቅን ፡ እየሰራህ ፡ ለምታኖረን (፪x)
እንዲያው ፡ ክበር ፡ እንጂ ፡ ሌላ ፡ ምን ፡ ይባላል
ጌታ ፡ ያንተ ፡ ፍቅር ፡ ክመታወቅ ፡ ያልፋል (፪x)

አዝ:- ዓይኖቼንም ፡ እያበራህ ፡ ጉልበቴንም ፡ እያጸናህ
ወደ ፡ ፊት ፡ እያራመድከኝ ፡ በድል ፡ ላይ ፡ ድልን ፡ ሰጠኅኝ
በእውነት ፡ አንተ ፡ ጌታ ፡ ነህ ፡ ምስጋናዬም ፡ ይድረስህ
በእውነት ፡ አንተ ፡ ንጉስ ፡ ነህ ፡ አምልኮዬም ፡ ይድረስህ

Recently Listened by

0 comments
    No comments found

:: / ::
::
/ ::

Queue