Emen bicha enji (እመን ፡ ብቻ ፡ እንጂ)

አዝ፦ ሰው ፡ ሁሉ ፡ ዓለሙን ፡ ቢያተርፍ
ነፍሱን ፡ ግን ፡ ባያድን ፡ ምን ፡ ይጠቅመዋል (፬x)

የሰው ፡ ድካሙ ፡ ለሥጋ ፡ ሆኖአል
አይ ፡ ነፍሱ ፡ ግን ፡ በርሃብ ፡ ጠውልጓል
ያከማቻውም ፡ ለሌላ ፡ ይሆናል
የደከመበትን ፡ ሳይበላ ፡ ይቀራል (፪x)

አዝ፦ ሰው ፡ ሁሉ ፡ ዓለሙን ፡ ቢያተርፍ
ነፍሱን ፡ ግን ፡ ባያድን ፡ ምን ፡ ይጠቅመዋል (፬x)

ፈጣሪህን ፡ አስብ ፡ በጉብዝናህ ፡ ወራት
ኃይል ፡ ከአንተ ፡ እርቆ ፡ ሳይጥልህ ፡ ጉልበት
ትእዛዙን ፡ ጠብቅ ፡ ፍራ ፡ እግዚአብሔርን
ነፍስህ ፡ ሳይመለስ ፡ ሥጋ ፡ ወደ ፡ አፈር (፪x)

አዝ፦ ሰው ፡ ሁሉ ፡ ዓለሙን ፡ ቢያተርፍ
ነፍሱን ፡ ግን ፡ ባያድን ፡ ምን ፡ ይጠቅመዋል (፬x)

በሕይወት ፡ ዘመንህ ፡ የሚሻልህን
እንዳትረዳው ፡ ጋርዶ ፡ የያዘህን
ዓይንህ ፡ ይገለጥ ፡ ከንቱ ፡ ነው ፡ ሁሉ
በዚህ ፡ ዓለም ፡ ላይ ፡ ያለው ፡ በሙሉ

በሕይወት ፡ ዘመንሽ ፡ የሚሻልሽን
እንዳትረጂው ፡ ጋርዶ ፡ የያዘሽን
ዓይንሽ ፡ ይገለት ፡ ከንቱ ፡ ነው ፡ ሁሉ
ከኢየሱስ ፡ ውጭ ፡ ያለው ፡ በሙሉ

አዝ፦ ሰው ፡ ሁሉ ፡ ዓለሙን ፡ ቢያተርፍ
ነፍሱን ፡ ግን ፡ ባያድን ፡ ምን ፡ ይጠቅመዋል (፬x)

Recently Listened by

0 comments
    No comments found

:: / ::
::
/ ::

Queue